የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ከሚሲዮኑ ሰራተኞች ጋር ተወያዩ፤

Compartilhar


ክቡር የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ዋሽንግተን ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች ጋር በሚሲዮኑ በመገኘት ውይይት ያካሄዱ ሲሆን በሚሲዮኑ ትኩረት ተሰጥቶ ሊተገበሩ በሚገባቸው እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ካነሷቸው ነጥቦች መሃከል ዲፕሎማቱና መላው ሰራተኛ በፖለቲካ ዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ፣ ሃብት ማፍራት፣ ወጪ ቅነሳ እንዲሁም ዲያስፖራ ጉዳዮችና ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በቡድን መንፈስ በመንቀሳቀስ የሚቆጠርና ውጤት ማስመዝገብ ላይ ትኩረት በማድረግ መሰራት እንደሚገባው አንስተዋል።

በኢትዮጵያ መንግስት እየተከናወኑ ያሉ ትልልቅ የልማት እንቅስቃሴዎችን በተገኘው አጋጣሚ ለአሜሪካ መንግስትና ባላብቶች እንዲሁም ለዲያስፖራው ማህበረሰብ በማስተዋወቅ የአገራችንን ገጽታ መገንባትና ኢንቨስተሮች ወደ አገራችን ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ በማስቻል ረገድ ትልቅ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።

በመጨረሻም ከሚሲዮኑ ሰራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ሰፋ ያለ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።



Source link

spot_img

Veja também

وزير العدل يتفقد سجني النساء ونواكشوط الجنوبية

أدى معالي وزير العدل السيد محمد ولد أسويدات،...

مؤتمر طوكيو الدّولي للتّنمية في إفريقيا

بتكليف من سيادة رئيس الجمهورية الأستاذ قيس سعيد...

الدبيبة يرحب باتفاق إنهاء الحرب في غزة ويشيد بجهود كافة الوسطاء لتحقيق هذا الاتفاق.

ليبيا/الدبيبة/غزة/وقف اطلاق النار/اتفاق/توقيع/ترحيـــــب/بيـان. Source link

Seychelles: líder da oposição vence eleições presidenciais

Em Seychelles, o líder da oposição, Patrick Herminie, venceu...
- Advertisement -spot_img